ክርስቲያናዊ ሕይወት
አምላክን የሚያስደስቱ ባሕርያትን አዳብሩ—ድፍረት
አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
-
ምሥራቹን መስበክ ድፍረት ይጠይቃል።—ሥራ 5:27-29, 41, 42
-
በታላቁ መከራ ወቅት ድፍረት የሚጠይቁ ነገሮች ያጋጥሙናል።—ማቴ 24:15-21
-
ሰውን መፍራት አሳዛኝ መዘዝ ያስከትላል።—ኤር 38:17-20፤ 39:4-7
ይህን ማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው?
ከአገልግሎት ጋር በተያያዘ የሚያስፈራኝ ነገር ምንድን ነው? እንዴትስ ልቋቋመው እችላለሁ?
ታማኝነትን የሚሸረሽሩ ነገሮችን አስወግዱ—ሰውን መፍራት የተባለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦
-
አገልግሎታችንን ለማከናወን ድፍረት የግድ አስፈላጊ ነው የምንለው ለምንድን ነው?
-
ምሳሌ 29:25 ላይ የትኞቹ ነገሮች በንጽጽር ቀርበዋል?
-
አሁኑኑ ድፍረት ማዳበር ያለብን ለምንድን ነው?