የሚስጥር አጠባበቅ ማስተካከያ

በjw.org ላይ ጥሩ የዲጂታል አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል ኩኪዎችንና ሌሎች ተመሳሳይ ቴክኖሎጂዎችን እንጠቀማለን። አንዳንድ ኩኪዎች ድረ ገጹ እንዲሠራ የግድ ስለሚያስፈልጉ መከልከል አይቻልም። አጠቃቀምህን ለማሻሻል ብቻ የምንጠቀምባቸውን ሌሎች ተጨማሪ ኩኪዎች መፍቀድ ወይም መከልከል ትችላለህ። ይህ መረጃ በፍጹም አይሸጥም ወይም ለንግድ ዓላማ አይውልም። ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ገጽ ተመልከት፦ የኩኪዎችንና ተመሳሳይ ቴክኖሎጂዎች አጠቃቀም ዓለም አቀፍ ፖሊሲ በማንኛውም ጊዜ ምርጫዎችን ማስተካከል ከፈለግክ ይህን ገጽ ተጠቀም፦ የሚስጥር አጠባበቅ ማስተካከያ

የጥናት ፕሮጀክት

ታማኝ ሰዎች ስእለታቸውን ይፈጽማሉ

ታማኝ ሰዎች ስእለታቸውን ይፈጽማሉ

መሳፍንት 11:30-40ን አንብብ፤ ከዚያም ስለ ዮፍታሔና ስለ ሴት ልጁ ከሚገልጸው ዘገባ ስእለት መፈጸምን በተመለከተ ምን ትምህርት እንደምናገኝ ለማስተዋል ሞክር።

አውዱን መርምር። ታማኝ የሆኑ እስራኤላውያን ለይሖዋ ስለሚገቡት ስእለት ምን ይሰማቸው ነበር? (ዘኁ. 30:2) ዮፍታሔና ልጁ በይሖዋ ላይ እምነት እንዳላቸው ያሳዩት እንዴት ነው?—መሳ. 11:9-11, 19-24, 36

በጥልቀት ምርምር አድርግ። ዮፍታሔ ስእለቱን የተሳለው ምን በአእምሮው ይዞ ሊሆን ይችላል? (w16.04 7 አን. 12) ስእለቱን ለመፈጸም እሱም ሆነ ልጁ የትኞቹን መሥዋዕቶች ከፍለዋል? (w16.04 7-8 አን. 14-16) በዛሬው ጊዜ ክርስቲያኖች ምን ዓይነት ስእለቶችን ሊሳሉ ይችላሉ?—w17.04 5-8 አን. 10-19

ትምህርቱን ለማስተዋል ሞክር። ራስህን እንዲህ እያልክ ጠይቅ፦

  • ‘ራሴን ስወስን የተሳልኩትን ስእለት መፈጸም የምችለው እንዴት ነው?’ (w20.03 13 አን. 20)

  • ‘ይሖዋን ይበልጥ በተሟላ ሁኔታ ለማገልገል ስል የትኞቹን መሥዋዕቶች መክፈል እችላለሁ?’

  • ‘የጋብቻ ስእለቴን ለመፈጸም ያለኝን ቁርጠኝነት ማጠናከር የምችለው እንዴት ነው?’ (ማቴ. 19:5, 6፤ ኤፌ. 5:28-33)